ሐሙስ 1 ጃንዋሪ 2015

“እኛና የኢትዮጵያውያን የጊዜ ቀመር”

ሮም በጥንታዊው የዓለም ታሪክ ውስጥ ግዙፍና ተጽዕኖ ፈጣሪ አገር እንደነበረች በየትኛውም የታሪክ ትምህርታችሁ
ሳይነገራችሁ አላለፈም፡፡ ይህች ታላቅ አገር የሥርዓትና የሕግ ሁሉ መፍለቂያ ነበረች፡፡ እዚያ የተወራው ተራ ወሬ በመላው ዓለም ርዕሰ ዜና ይኾን ነበር፡፡ ሮም ትኩሳት ከተነሣባት መላው ዓለም በረዶ መነከር ይጀምራል፡፡ ሮምን ጉጠት ጋጥ ካደረጋት መላው ዓለም በንፍፊት ያልቃል፡፡ ብቻ ምን አለፋችሁ ሮም የረጨችው ደም ነው ደም ኹኖ የቀረውን ዓለም በሁለት እግሩ አቁሞ እንደሰው የሚያራምደው፡፡ ታዲያ የታሪክ ጠበብት
ናቸው እንጂ እኔ እንደዚህ አላልኩም፡፡   

ዘመን ሲቈጠር ሲቈጠር ኖረና ልክ ከክርስቶስ ልደት በኋላ በ532 ዓ.ም. ላይ ከዚህች ከትኩሳት አገር አንድ መነኩሴ ተነሣና ዐይን የሚያስፈጥጥ አንዳች ክስ አቀረበ፡፡ ክሱ ጠንከር ያለና ባለፈው ትውልድ ላይ ኹሉ የተሰነዘረ ነበር፡፡ መነኩሴው ዲዮኒሰስ ኤግዚጉኒስ ይባላል አሉ፡፡ ይህን ክሱን

ማክሰኞ 9 ሴፕቴምበር 2014

እንኳን ለአዲሱ ዓመት አደረሳችሁ፡ “እኛና የኢትዮጵያውያን የጊዜ ቀመር”



ሮም በጥንታዊው የዓለም ታሪክ ውስጥ ግዙፍና ተጽዕኖ ፈጣሪ አገር እንደነበረች በየትኛውም የታሪክ ትምህርታችሁ ሳይነገራችሁ አላለፈም፡፡ ይህች ታላቅ አገር የሥርዓትና የሕግ ሁሉ መፍለቂያ ነበረች፡፡ እዚያ የተወራው ተራ ወሬ በመላው ዓለም ርዕሰ ዜና ይኾን ነበር፡፡ ሮም ትኩሳት ከተነሣባት መላው ዓለም በረዶ መነከር ይጀምራል፡፡ ሮምን ጉጠት ጋጥ ካደረጋት መላው ዓለም በንፍፊት ያልቃል፡፡ ብቻ ምን አለፋችሁ ሮም የረጨችው ደም ነው ደም ኹኖ የቀረውን ዓለም በሁለት እግሩ አቁሞ እንደሰው የሚያራምደው፡፡ ታዲያ የታሪክ ጠበብት

ማክሰኞ 19 ኦገስት 2014

(የልጅነት ወግ) ቡሄ ሲመጣ እኔን ትዝ የሚለኝ



አይ ልጅነት! አይ ሆያ ሆዬ! አይ ያሚ ሜዳ … አይ ሞደርን ሰፈር፡፡ አይ ጥይት ቤት .. አይ አይ አይ … ሙልሙል በችርቻሮ የሸጥንበት ጊዜ … 
 
የምንጨፍርበት ዱላችን ከምት ብዛት ሥሩ ሥር ያበቀለ እስኪመስል ጭራሮ ኾኖ፡፡ ዱላ እጁ ላይ ያለቀበት ጨፋሪ እኮ ነበረ መሃላችን፤ … የገነት አቡሽ፡፡ ጠዋት መጨፈር የጀመርን ሰዓት በጨመረ ቁጥር ዱላው እያጠረ፣ እሱም እያጎነበሰ … ማታ ላይ አቡሽ ለምንጨፍርበት ቤት ቤተኞች የአክብሮት ሰላምታ እየሰጠ እንጂ እየጨፈረ በፍጹም አይመስላቸውም ነበር፡፡ እሱም ግን መሬቱን በጣም

Comment on this