ታዋቂ ልጥፎች

ገፆች

2015 ጃንዋሪ 1, ሐሙስ

“እኛና የኢትዮጵያውያን የጊዜ ቀመር”

ሮም በጥንታዊው የዓለም ታሪክ ውስጥ ግዙፍና ተጽዕኖ ፈጣሪ አገር እንደነበረች በየትኛውም የታሪክ ትምህርታችሁ
ሳይነገራችሁ አላለፈም፡፡ ይህች ታላቅ አገር የሥርዓትና የሕግ ሁሉ መፍለቂያ ነበረች፡፡ እዚያ የተወራው ተራ ወሬ በመላው ዓለም ርዕሰ ዜና ይኾን ነበር፡፡ ሮም ትኩሳት ከተነሣባት መላው ዓለም በረዶ መነከር ይጀምራል፡፡ ሮምን ጉጠት ጋጥ ካደረጋት መላው ዓለም በንፍፊት ያልቃል፡፡ ብቻ ምን አለፋችሁ ሮም የረጨችው ደም ነው ደም ኹኖ የቀረውን ዓለም በሁለት እግሩ አቁሞ እንደሰው የሚያራምደው፡፡ ታዲያ የታሪክ ጠበብት
ናቸው እንጂ እኔ እንደዚህ አላልኩም፡፡   

ዘመን ሲቈጠር ሲቈጠር ኖረና ልክ ከክርስቶስ ልደት በኋላ በ532 ዓ.ም. ላይ ከዚህች ከትኩሳት አገር አንድ መነኩሴ ተነሣና ዐይን የሚያስፈጥጥ አንዳች ክስ አቀረበ፡፡ ክሱ ጠንከር ያለና ባለፈው ትውልድ ላይ ኹሉ የተሰነዘረ ነበር፡፡ መነኩሴው ዲዮኒሰስ ኤግዚጉኒስ ይባላል አሉ፡፡ ይህን ክሱን

Comment on this